ትንሿ ደሴት ለ2026 የዓለም ዋንጫ አለፈች

Date:



በካሪቢያን ባህር የምትገኘው እና በትንሽ የህዝብ ቁጥር የምትታወቀው ኩራሳኦ ለ2026ቱ የፊፋ የዓለም ዋንጫ ማለፏን አረጋገጠች።

ኩራሳኦ ወደዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ የደረሰችው ወሳኝ በተባለው የመጨረሻ የማጣሪያ ጨዋታ ከጠንካራዋ ጃማይካ ጋር 0-0 በሆነ ውጤት በመለያየት ነው።

ይህ ውጤት በምድብ “2” አንደኛ ሆና እንድታጠናቅቅ እና በቀጥታ ወደ አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ የዓለም ዋንጫ እንድታመራ አስችሏታል።

185,000 የሚጠጋ የህዝብ ቁጥር ያላት ኩራሳኦ ለአለም ዋንጫ ማለፍ የቻለች ትንሿ ሀገር በመሆን አዲስ ታሪክም መጻፍ ችላለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...