ፌዴራል ፖሊስ ከተባበሩት መንግሥታት የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን በድጋፍ አገኘ

Date:

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ከተባበሩት መንግሥታት የሴፍቲና የሴኩሪቲ ዲፓርትመንት ለወንጀል መከላከል ሥራ አጋዥ የሆኑ ዘመናዊ ኮምፒውተሮችንና የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን በድጋፍ ማግኘቱን አስታወቀ።

ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወነው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት፣ የዲፓርትመንቱ ኃላፊ ሚስተር ፕሪንስ ብሩስ መሣሪያዎቹን ለፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፋንታ አስረክበዋል።

ምክትል ኮሚሽነሩ በዚሁ ወቅት በድጋፍ የተገኙት ቁሳቁሶች ተቋሙ እያከናወነ ላለው የወንጀል መከላከል ተግባር ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖራቸው ገልፀዋል።

የዲፓርትመንቱ ኃላፊ ሚስተር ፕሪንስ ብሩስ በበኩላቸው፤ ተቋማቸው ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ድጋፍ በማድረጉ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው፣ በቀጣይም በወንጀል መከላከል ዙሪያ በትብብር ለመሥራትና ሌሎች መሰል ድጋፎች እንደሚደረጉ መናገራቸውን ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...