በሶማሊያው ፕረዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ ላይ የቦምብ ጥቃት ደረሰባቸው

Date:

ሁለት ከፍተኛ የመንግስት እና ወታደራዊ ባለስልጣናት ለሮይተርስ እንዳረጋገጡት ፕረዚዳንቱ ጥቃቱን ተከትሎ ደህና መሆናቸውን  ገልጸዋል።

ጥቃቱን የተመለከቱ ወታደሮች እና የአካባቢው ነዋሪዎች የፕረዚዳንቱ ኮንቮይ መምታቱን አረጋግጠዋል።  የሮይተርስ ጋዜጠኛ በቦታው በተገኘበት ሰዓትም በፕረዚዳንቱ ቤተ መንግስት አካባቢ በደረሰው ጥቃት የአራት ሰዎች አስከሬንን መመልከት ችሏል።

አልሸባብ ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ባለው የቴሌግራም ቻናል ላይ ባሰፈረው መግለጫ “የእኛ ተዋጊዎቻችን ሀሰን ሼክ መሀመድን የጫኑ ተሽከርካሪዎች ከፕሬዚዳንት ቤተ መንግስት ለቀው ወደ አየር ማረፊያ ሲሄዱ ኢላማ አድርገናቸዋል” ይላል።

የሶማሊያ መንግስት ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ መፈጸሙን ገልጾ ፕረዚዳንቱ ግን ሰላም መሆናቸውንና በጉዟቸውም አልሸባብን እየተዋጋበት በሚገኘው በመካከለኛው ሸበሌ አደን ያባል ግዛት ካሉ ወታደሮችን ጋር አቦሮ ለማፍጠር እንደነበርና በቦታውም እንደተገኙ ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...