ከአክሱም እስከ አሜሪካ የመንትዮቹ የህክምና ጉዞ!

Date:

ተጣብቀው ተወልደው ለሁለት ዓመታት ያህል አንድ ላይ የቆዩት ተአምረኞቹ መንትዮች ህያብ እና ወህብቶ በአሜሪካ በሚገኘው ሴይንት ሉዊስ ሆስፒታል በተደረገላቸው እጅግ ውስብስብ ቀዶ ህክምና በስኬት መለያየታቸው ተበሰረ።

ታሪኩ የሚጀምረው መጋቢት 2016 ዓ.ም በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ኮንፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ነው።

ህያብ እና ወህብቶ ተጣብቀው ወደዚህች ዓለም ሲቀላቀሉ ቤተሰቦቻቸው በደስታ እና በስጋት መካከል ነበሩ።

ሆስፒታሉ ለ8 ወራት ያህል ልዩ እንክብካቤ ሲያደርግላቸው የቆየ ቢሆንም የቤተሰቦቻቸው የኢኮኖሚ አቅም ግን ለቀጣዩ ከባድ ህክምና ፈታኝ ነበር። የመንትዮቹ ቤተሰቦች በኢኮኖሚ አልደረጁም።

በመቐለ የሚገኘው ሎላ የህፃናት ማሳደጊያ ማዕከል የህፃናቱን ሁኔታ ተረድቶ ኃላፊነቱን በመውሰድ ተጨማሪ የህክምና ዕድሎችን መፈለግ ጀመረ።

ጥረቱም ፍሬ አፍርቶ በአሜሪካ ነዋሪ የሆኑት ፕሮፌሰር ሙሉጌታ ባደረጉት ከፍተኛ እገዛ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ህፃናቱ ወደ አሜሪካ ሚዙሪ ግዛት አቀኑ።

ባለፉት ወራት ህፃናቱ በሴይንት ሉዊስ ሆስፒታል አራት ተከታታይ እና ከባድ የቀዶ ህክምናዎችን አልፈዋል።

በመጨረሻም የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም አምስተኛው እና ወሳኙ የቀዶ ህክምና ስራ ተከናወነ።

በዚህም ለሁለት ዓመታት ተጣብቀው የነበሩት ህፃናት በሰላም ተለያዩ።

የህፃናቱ አባት አቶ ሙኡዝ አብርሃ ከአሜሪካ ሆስፒታል ባስተላለፉት መልእክት፣ ” ህክምናው ተሳክቶ ህያብና ወህብቶ በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ” በማለት አብስረዋል።

ይህ ስኬት የህክምና ጥበብ ውጤት ብቻ ሳይሆን የሰው ልጆች ርህራሄ እና ትብብር ምን ያህል ተአምር እንደሚሰራ የታየበት ደማቅ ታሪክ ነው።

ቲክቫህ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...