የኢራን ጦር አዛዥ አሚር ሃታሚ በእስራኤል የአየር ጥቃት የደህንነት ኃላፊው አሊ ላሪጃኒን መገደላቸውን ተከትሎ “ወሳኝ” የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስዱ አስጠነቀቁ።
“ለወንጀለኛዋ አሜሪካ እና ደም የተጠማው የጽዮናውያን አገዛዝ በተገቢው ጊዜና ቦታ፣ ወሳኝ፣ የሚያሽመደምድ፣ ጸጸት ውስጥ የሚጥል ምላሽ እንሰጣለን” ሲሉ ሃታሚ በሰጡት መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
የላሪጃኒ እና የሌሎች “ሰማዕታት ሞት እንበቀላለን” በማለት አክለዋል።
ከጦር ኃይሉ የተለየ ወታደራዊ አካል የሆነው የኢራን አብዮታዊ ዘብ የላሪጃኒን ሞት “ለመበቀል” ወደ ማዕከላዊ እስራኤል ሚሳኤሎችን መተኮሱን የኤኤፍፒ የዜና ወኪል ዘግቧል።
