የኢራን መርከቦች የአሜሪካን እገዳ ለመስበር አዳዲስ ስልቶችን እየተጠቀሙ ነው

Date:

አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን የባሕር ላይ እገዳ ተከትሎ፣ ከቴህራን ጋር ግንኙነት ያላቸው መርከቦች በሆርሙዝ የባሕር መስመር ላይ ክትትልን የሚያሳስቱ የቴክኖሎጂ ስልቶችን በስፋት እየተጠቀሙ መሆኑን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል።

መርከቦቹ መገኛቸውን የሚያሳውቁ መሣሪያዎችን በማጥፋት ራሳቸውን ከራዳር ይሰውራሉ፤ አልያም ደግሞ የተሳሳተ መረጃ በመላክ ሌላ መርከብ መስለው ለመታየት ይሞክራሉ።

የባሕር ላይ ደህንነት ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ፣ መርከቦቹ የክትትል ቀጠናውን ለማለፍ የሐሰት መታወቂያዎችን በመጠቀም አሜሪካ የጣለችውን ጥብቅ ቁጥጥር እየተፈታተኑት ይገኛሉ።

ይህ አይነቱ የማታለል ስልት ቀደም ሲል በሩሲያ መርከቦች ላይ ይስተዋል የነበረ ሲሆን፣ አሁን ግን በሆርሙዝ የባሕር መስመር ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ታውቋል።

ይህም የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ በትክክል ለመከታተል አስቸጋሪ ከማድረጉም ባለፈ፣ በዓለም አቀፍ የውኃ መስመር ላይ ከፍተኛ አለመረጋጋትና እርግጠኛ አለመሆንን እየፈጠረ ነው።

መርከቦቹ እንዲህ ያለውን አደገኛ የ”ድብብቆሽ” ጨዋታ የሚጫወቱት የአሜሪካን ወታደራዊ እገዳ ጥሰው የነዳጅና የምግብ ምርቶችን ለማጓጓዝ መሆኑን የባሕር ላይ መረጃ ተንታኞች ገልጸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...