የፓኪስታን ልዑካን ቡድን ቴህራን ደረሰ

Date:

አሜሪካን እና ቴህራንን እያሸማገለ የሚገኘው የፓኪስታን ልዑካን ቡድን ቴህራን ገባ።

ከልዑካን ቡድኑ መካከል ከዚህ ቀደም ትራምፕ “የምወደው” ሲሉ የገለጿቸው ፊልድ ማርሻል አሲም ሙኒር እና የአገር ውስጥ ሚኒስትሩ ሞሺን ናቅቪ እንደሚገኙበት በመንግሥታቱ ድርጅት የፓኪስታን ተልዕኮ መግለጫ ያስረዳል።

ቀደም ሲል የኢራን መገናኛ ብዙኃን፣ ኢሪብ የዜና ወኪል የአሜሪካን መልዕክት ለማስተላለፍ እና ስለሁለተኛው ዙር ድርድር ለመነጋገር የልዑካን ቡድን ወደ ቴህራን እንደሚመጣ ዘግቦ ነበር።

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመርያውን ዙር ድርድር ባለፈው ሳምነት መጨረሻ ላይ በኢዝላማባድ ያደረጉ ሲሆን ያለምንም ውጤት ተጠናቅቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሙሐማድ ሼህባዝ ሻሪፍ ሳዑዲ አረቢያ፣ ጂዳ ደርሰዋል።

ጽህፈት ቤታቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ አገራት የተጓዙት “በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ ለመለዋወጥ” መሆኑን ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...