Date:

ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ!

አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ ጨዋታ፣ መላው የስፖርት ቤተሰብ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የከተማው ደርቢ ተጠናቀቀ።

በታላቁ የአዲስ አበባ ስታዲየም የተካሄደው የሁለቱ ግዙፎች ፍልሚያ፣ የኢትዮጵያ ቡናን የላቀ የበላይነት ባሳየ መልኩ በኢትዮጵያ ቡና 3 – 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በጨዋታው ኢትዮጵያ ቡና በወጣትና ፈጣን የቡድን ስብስቡ በመታገዝ የጨዋታውን ብልጫ በመውሰድ ነጥቡን ማሳካት ችሏል።

የግብ አግቢዎች፤ ለኢትዮጵያ ቡና፡- ኦካይ ጁል፣ ቢኒያም ጌታቸው እና ዘላለም አባተ

ለቅዱስ ጊዮርጊስ፡- ፍፁም ጥላሁን

በዛሬው ዕለት የሸገርን አውራ ጎዳናዎች በቡናማ እና አረንጓዴ/ቢጫ ቀለም በድምቀት ያጥለቀለቁት ደጋፊዎች፣ ጨዋታው ከሶስት ነጥብ በላይ የክብርና የኩራት ፍልሚያ መሆኑን ዳግም አስመስክረዋል።

ቡናማዎቹ በታክቲክ ብልጫና በቁርጠኝነት ያሳዩት ብቃት ውጤቱን እንዲቀዳጁ አድርጓቸዋል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በዓለም ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 2ኛ የወርቅ ሜዳሊያ አገኝች

በሴቶች 3 ሺህ ሜትር የተወዳደሩት  ዮርዳኖስ ጽጋብ እና ሽቶ...

“አዳም አንድ ደራሲ የሚያስፈልጉት ሁሉም ግብዓቶች ተሟልተው ያሉት ፀሐፊ ነው”

አዳም ረታ ሥራዎቹን ለአንባቢ ማድረስ የጀመረው ከ1970ዎቹ አንስቶ ነው።...

ከፍተኛ የግብር ክፍያ በሕጋዊ ነጋዴው ላይ በመጫን ሲፈጽሙት …

መንግስት ከግብር የሚያገኘው ገቢ የቀነሰው ወይም ከሀገር ውስጥ አጠቃላይ...

ሆስፒታሊቲ እና ቱሪዝም እውቅና እና ሽልማት መርሃ-ግብር ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

የአዲስ አበባ ሆቴል እና ቱሪዝም ባለሙያዎች ማኅበር ሁለተኛውን የሆስፒታሊቲ...