ከ10 በላይ የሚሆኑ ተጠርጣሪዎች ማክሰኞ ምሽት በክሌቭላንድ ወደሚገኘው ጁምፐርስ ኢ-መደበኛ የሰፈራ መንደር (የጨረቃ ቤቶች የሚገኙበት ሰፈር) በመዝለቅ፣ በተለያዩ ቦታዎች በነዋሪዎች ላይ ተኩስ ከፍተው ከአካባቢው መሰወራቸውን የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አገልግሎት አስታውቋል።
ስምንት ወንዶች እና ሦስት ሴቶች ጥቃቱ በተፈፀመበት ቦታ ሕይወታቸው ማለፉ ሲረጋገጥ፣ ሌላ አንድ ወንድ ሰለባ ደግሞ በደረሰበት ጉዳት ሆስፒታል ውስጥ ሕይወቱ አልፏል።
ባለሥልጣናት ተጠርጣሪዎችን ለማደን ፍለጋ ጀምረዋል። የጥቃቱ መንስኤ አልታወቀም፤ እስካሁን የተያዘም ተጠርጣሪም የለም።
