የዘመኑ ወላጆች ጭንቀት “በእዚህ በዘመናዊው ዓለም ልጆቻቸው ተጠልፈው ከሃይማኖት እንዳይወጡ እንዴት እንጠብቅ?” የሚለው ነው።
ይኽንን ችግር ለመፍታት በመጪው ክረምት ከ12 እስከ 17 ዓመት ላሉ ለልጆች በእንግሊዝኛ ቋንቋ የሚሰጥ ትምህርት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስትያን መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/ አዘጋጅነት ሊጀመር ነው።
ትምህርቱ ቅዳሜ ሰኔ 27(July 4) ጀምሮ እስከ እሑድ ሐምሌ 26(August 2) በሳምንት ሁለት ቀን ቅዳሜና እሑድ ከ8 ሰዓት እስከ 10:30 ለአራት ተከታታይ ሳምንታት የሚሰጥ ሲሆን፤ በቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ-ክርስትያን/ ገርጂ ማርያም የሚካሄድ ይሆናል።
ትምህርቱ ያለምንም ክፍያ የሚሰጥ ቢሆንም ያለው ቦታ ውሱን በመሆኑ በጊዜ ለመመዝገብ ከታች ያለውን link በመጠቀም ይመዝገቡ።
