ሁቲዎች በሳዑዲ አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

Date:

የየመን ሁቲ አማጺያን የሳዑዲ አረቢያን አውሮፕላን ማረፊያዎች እና ሌሎችም ቁልፍ ሥፍራዎችን የጥቃት ዒላማ እንደሚያደርጉ ዛቱ።

ሁቲዎች፤ የኢራን የሲቪሎች አውሮፕላን በሰንዓ አውሮፕላን ማረፊያ እንዳያርፍ ከልክለዋል ካሏቸው “የሳዑዲ ተዋጊዎች” ጋር ግጭት ውስጥ መግባታቸውን ገልጸዋል።

የሁቲ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ያህያ ሳሬ፤ ሳዑዲ “የየመንን የአየር ክልል መጣስ የምትቀጥል ከሆነ በየብስ እና በባሕር ላይ ያሉ ቁልፍ ሥፍራዎችን እና አውሮፕላን ማረፊያዎችን የጥቃት ዒላማ” እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ውዝግቡ እንዳለ ሆኖ በሰንዓ እና ቴህራን መካከል ያለው በረራ መቀጠሉን ተናግረዋል።

በሳዑዲ የሚመራው ጥምር፣ ሁቲዎች ላወጡት መግለጫ በሰጠው ምላሽ “መግለጫው ቡድኑ በየመን ሕዝብ ላይ የሚፈጽመውን ድርጊት ትኩረት ለማስለወጥ ያለመ ነው” ብሏል።

ለሁቲ ቅርበት ያለው አል-ማሲራህ ቴሌቭዥን እንደዘገበው፤ የኢራን አውሮፕላን ሰንዓ የደረሰው ትናንት አርብ ነው።

የሁቲ ልዑካንን ወደቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት ለመውሰድ አውሮፕላኑ መጓዙ ተገልጿል።

ሳዑዲ የምትመራው ጥምር ጦር በበኩሉ የሳዑዲን አልያም የየመንን ሉዓላዊነት የሚገዳደር ሙከራ ላይ “ጠንካራ እርምጃ” እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

ከአውሮፓውያኑ 2015 ጀምሮ ጦሩ በየመን ጦርነት ውስጥ ተሳትፎ ማድረጉን ቀጥሏል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“የድንቁርና” እና “የታሪክ ፍልሠትን” የሚያስከትል ድርጊት ነው

የቅዱስ ላሊበላ ገዳም ዓለማቀፍ ቅርስ አሥተዳደር ጽሕፈት ቤት፣...

በመቐለ ከተማ በወጣቶች ላይ “የግዳጅ አፈሳ” ተጀምሯል

በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ የጸጥታ ኃይሎች በወጣቶች ላይ...

በትምህርት ቤቶች ዙሪያ የትንባሆ መሸጫ ክልከላ ርቀት ወደ 500 ሜትር ከፍ ተደረገ

የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን በትምህርት ቤቶች ዙሪያ የትንባሆ...

አዲሱን የጉምሩክ አዋጅ የባለንብረቶችን ሥጋት ሊፈታ እንደሚገባ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሠሪዎች ፌዴሬሽን፤ አዲሱን የጉምሩክ አዋጅ ለማስፈጸም የሚወጣው...