ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

Date:

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም በነበሩት ሶስት ወራት ውስጥ በኢትዮጵያ ለሚገኘው የቴሌኮም ድርጅቱ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን የኬንያ ሺሊንግ በካፒታል መልክ ማፍሰሱን ገለጸ።

ድርጅቱ ባወጣው አዲስ ይፋዊ መግለጫ መሠረት፣ በኢትዮጵያ ለሚንቀሳቀሰው ቅርንጫፉ ያደረገው ጠቅላላ የፋይናንስ አስተዋፅኦ ባለፈው መጋቢት ወር ከነበረበት 158.2 ቢሊዮን ሺሊንግ (1.223 ቢሊዮን ዶላር)፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ወደ 159.6 ቢሊዮን ሺሊንግ (1.234 ቢሊዮን ዶላር) አድጓል።

ይህ የካፒታል ጭማሪ ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ባለው የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለውን ከፍተኛ ትኩረትና ቁርጠኝነት ያሳያል ተብሏል።

ኩባንያው ይህንን ስራ የሚከውነው ከዋናው ባለድርሻ ቮዳኮም፣ ከሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን፣ ከብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን  ጋር በጋራ በመሆን ነው።

ይህ ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ድርጅቱ በአገሪቱ የሚያደርገውን የኔትወርክ ማስፋፊያ፣ የአገልግሎት ጥራት ማሻሻል እና የደንበኞችን ቁጥር የማሳደግ ስራ በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል የሚረዳው መሆኑ ተመልክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...