ፕሮፌሰር አማረ አበበ በአፍሪካ ተወዳዳሪ እና ቅንጅታዊ የሥነ-ፈለክ ማሕበረሰብ የመፍጠር ዓላማ ያለውን ተቋም እንዲመሩ ተመርጠዋል።
በደቡብ አፍሪካ የሰሜን ምዕራብ ዩኒቨርሲቲ የጠፈር ምርምር ማዕከል የምርምር ዳይሬክተር የሆኑት ፕሮፌሰር አማረ አበበ፤ በአዲሱ የሥራ ኃላፊነታቸው የተቋሙን አባላት ቁጥር መጨመር እና የምርምር ትብብርን ማጎልበት እና በአፍሪካ የሥነ-ፈለክ ትምህርትን ማሳደግ ላይ እንደሚሠሩ ገልፀዋል።
@sputnik_ethiopia
