በካናዳ የተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት

Date:

በካናዳ ማኒቶባ ክፍለ ሃገር የተቀሰቀሰው ሰደድ እሳት በፍጥነት በመዛመት ላይ መሆኑ ተገልጿል።

የህይወት አድን ሰራተኞች የጦር አውሮፕላኖችን እና ሄሊኮፕተሮች በመጠቀም ነዋሪዎችን ከአካባቢው በማሸሽ ላይ ይገኛሉ።

በምዕራብ ካናዳ ሳስካችዋን እና ማኒቶባ አካባቢዎች እስካሁን በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መኖሪያቸውን ለቅቀው እንዲወጡ መደረጉም ታውቋል።

በአካባቢዎቹ ለአንድ ወር የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን የአካባቢው ባለስልጣናትም ተጨማሪ የእሳት አጥፊ ባለሙያዎች ላኩልን ጥሪ ለዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ ማስተላለፉቸው ተነግሯል።

በአካባቢዎቹ በቀጣይ ቀናት ደረቅ እና ሞቃታማ የዓየር ንብረት እንደሚኖር መተንበዩን ተከትሎ ሰደድ እሳቱን የመቆጣጠር ሥራው ይቀልጥ ፈታኝ እንዳይሆን መሰጋቱን ቢቢሲ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...