ለሰላም ድርድሩ ዶናልድ ትራምፕ እና ቭላድሚር ፑቲን መገናኘታቸው ግድ ነው

Date:

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማርኮ ሩቢዮ በቱርክ በሚካሄደው የዩክሬን-ሩሲያ የሰላም ድርድር ብዙ ተስፋ እንደሌላቸው እና ለውጥ እንዲኖር ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን መገናኘታቸው አስፈላጊ መሆኑን ተናገሩ።

በደቡባዊ ቱርክ የሰሜን ጦር ቃል ኪዳን አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ላይ ከተገኙ በኋላ “ፕሬዚዳንት ትራምፕ እና ፑቲን በቀጥታ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ እስካልተወያዩ ድረስ እዚህ ለውጥ የምናገኝ አይመስለኝም” ብለዋል።

ቮሎድሚር ዜሌንስኪ አገራቸው በኢስታንቡል ለሚደረገው ውይይት ልዑካንን እንደምትልክ አረጋግጠው፤ ነገር ግን በሞስኮ የተላከውን “ዝቅተኛ ደረጃ” ያለው ልዑካን ነው ሲሉ ነቅፈዋል።

የፑቲን የቅርብ ረዳት የሆኑት ቭላድሚር ሜዲንስኪ በቡላቸው የክሬምሊን ቡድን “ሁሉም አስፈላጊ ብቃቶች” እንዳለው ተናግረዋል።

መካከለኛው ምሥራቅን እየጎበኙ ያሉት ትራምፕ ቀደም ብለው እርሳቸው እና ፑቲን በአካል እስኪገናኙ ድረስ በሰላማዊ ንግግሮቹ ላይ ከፍተኛ መሻሻል የማይታሰብ መሆኑን ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...