ሰባት የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በደቡብ አፍሪካ ጠፉ

Date:

የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ለ2019 (እ.ኤ.አ 2027) የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ታሪካዊ በሆነ ሁኔታ ለምድብ ድልድል ካለፈ በኋላ፣ ሰባት ተጫዋቾች ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆኑ በደቡብ አፍሪካ መቅረታቸውን ቢኤስኤን ስፖርትስ ዘግቧል።

​ይህ ክስተት የተሰማው ኤርትራ በድምር ውጤት ኤስዋቲኒን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ፣ ከ19 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል መሸጋገሯን ካረጋገጠች ጥቂት ቆይታ በኋላ ነው።

​እንደ ዘገባው ከሆነ ለጨዋታው ወደ ደቡብ አፍሪካ ከተጓዙት አሥር በአገር ውስጥ የሚጫወቱ ተጫዋቾች መካከል ወደ ኤርትራ የተመለሱት ሦስቱ ብቻ ናቸው። ወደ ሀገራቸው የተመለሱት ተጫዋቾች አብሌሎም ተክለዝጊ፣ ናሆም ታደሰ እና ሮሜል አብዱ ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ ሰባት ተጫዋቾች በደቡብ አፍሪካ መቅረታቸው ተነግሯል።

​ይህ ድርጊት የኤርትራ ስፖርተኞች ለዓለም አቀፍ ውድድሮች ወደ ውጭ ሀገራት በሚጓዙበት ወቅት የግል እና ፖለቲካዊ ምክንያቶችን በመጥቀስ በዚያው የመቅረት (ጥገኝነት የመጠየቅ) ልማዳቸው ላይ አዲስ ስጋትን ፈጥሯል።

​ኤርትራ ወደ ምድብ ድልድሉ ማለፏ ለሀገሪቱ የእግር ኳስ እድገት ትልቅ ስኬት ተደርጎ ሲወደስ የቆየ ቢሆንም፣ የተጫዋቾቹ ድንገተኛ መሰወር ለቡድኑ ከፍተኛ እንቅፋት እንደሚሆን ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...