በትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

Date:

በደቡብ ጎንደር ዞን በይፋግ ንዑስ ፖሊስ ጣቢያ በደረሰ የትራፊክ አደጋ፤ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

አደጋው የደረሰው 18 ሰዎችን አሳፍሮ ከጎንደር ወደ ባህር ዳር የሚጓዝ አነስተኛ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ፤ ልዩ ቦታው አምባርጌ ዘይት ፋብሪካ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቆመ ኤፍ ኤስ አር የጭነት መኪና ጋር ተጋጭቶ በመገልበጡ ነው ተብሏል።

በአደጋውም አሽከርካሪውን ጨምሮ የ7 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፤ የይፋግ ንዑስ ፖሊስ ጣቢያ የመንገድ ትራፊክ ተቆጣጣሪ ባለሙያ ዋና ሳጅን ያለው ሞላ ተናግረዋል።

በተጨማሪም 7 ከባድ እና 4 ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎችን የአካባቢውን ሕዝብ በማስተባበር አዲስ ዘመን ሆስፒታል መወሰዳቸውን ገልጸዋል።

አደጋው የደረሰው ከተፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር መሆኑን ያነሱት ዋና ሳጅን ያለው፤ “አሽከርካሪዎች ሕግና ስርዓትን አክብረው በማሽከርከር በሰው ሕይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ መከላከል ይገባል” ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

(አሐዱ ሬድዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...