በኢትዮጲያ የሚገኙ የደም ባንኮች ቁጥር 59 ደረሰ

Date:

በተለያዩ ክልሎች ሙሉ አቅም አዳዲስ የደም ባንኮች  እየተገነቡ መሆኑን እና ይህም የበጎ ፍቃድ ደም ለጋሾችን ቁጥር በማሳደግ በደም እጥረት ጉዳት እንዳይደርስ ከማድረጉም ባሻገር  የደም ባንክን ተደራሽነት ይጨምራል ሲሉ የኢትዮጲያ ደም እና ህብረህዋስ ባንክ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ታረቀኝ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

በኢትዮጲያ ተጨባጭ ሁኔታ በደም ባንክ ተደራሽነት ላይ ወደ ፊት በጥናት እየታየ መሰራት አለበት ያሉት አቶ አለማየሁ በዘንድሮ በጀት አመት በ3 ክልሎች ብቻ በራስ አቅም 10 የደም ባንኮችን ለመገንባት ታቅዶ 6 ያህሉን አጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ተሰርገዋል።

የአሮሚያ ክልል በዘንድሮው የበጀት አመት አራት የደም ባንኮችን ለመገንባት አቅዶ የደምቢ ዶሎና  የሻምቡ የደም ባንኮችን አስመርቆ ለአገልግሎት ማብቃቱን ገልፀው፤በተመሣሣይ የሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት  በክልሉ የሚገኙትን የደም ባንኮች ቁጥር ከ7 ወደ 12 ለማድረስ አቅዶ ፊልቱ፣ ቀብሪደሃርና  ገርቦ የደም ባንኮችን የገነባ ሲሆን የአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስትም የአብአላ ደም ባንክን በመገንባት በክልሉ የሚገኙ የደም ባንኮች ቁጥር 3 ማድረስ ተችሏል።

በአጠቃላይ የደም ባንኮች ግንባታ በሀገሪቱ የሚገኙ የደም ባንኮችን ቁጥር ወደ 59 ማድረሱን የጠቆሙ ሲሆን ይህም በጎ ፍቃድ ደም ለጋሾች በአቅራቢያቸው በመሄድ ደም በመለገስ በደም እጦት ምክንያት ሊጠፉ የሚችሉ ህይወቶችን ለመታደግ አስቻይ ሁኔታ እንደሚፈጥርላቸው እና የሀገሪቱ የጤና ሥርዓት መሻሻል አዎንታዊ ሚና እንዳለዉ ተመላክቷል፡፡

#BisratRadio

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...