የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሐውስ እንደሚገናኙ አስታወቀ።
ኔታንያሁ እና ትራምፕ እንደሚወያዩ ይፋ የተደረገው ከኢራን ጦርነት ጋር በተያያዘ የሁለቱ መሪዎች ግንኙነት በሻከረበት ወቅት ነው።
የኔታንያሁ ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ “በዚህ ጉዞ ማክሰኞ ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዋይት ሐውስ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር ይገናኛሉ። የእስራኤል ወዳጅ የነበሩት ሴናተር ሊንዚ ግርሃምን የቀብር ሥነ ሥርዓትም ይታደማሉ” ብሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ወደ ዋሽንግተን ጉዟቸውን የሚጀምሩት ሰኞ እንደሆነም ተገልጿል።
