የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዛሬ መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሚሰጣቸው የባንኩ አገልግሎቶች ላይ ደንበኞቹ የሚከፍሉት ክፍያ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ የተጨመረ መሆኑን ደንበኞቼ ሊያውቁት ይገባል ሲል ገለጸ። ባንኩ ተጨማሪ እሴት ታክስ እያስከፈለ የሚገኘው መንግስት በቅርቡ ባወጣው አዲስ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሕግ መሰረት መሆኑን አመላክቷል። ባንኮች በሚሰጧቸው አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲጣል መንግስት ባሳለፍነው አመት መጨረሻ አዋጅ ማውጣቱን ያወሳው ንግድ ባንክ ይህንን የተጣለውን ግዴታ ለመወጣት በሚል ከመስከረም 21 ቀን 2017 ዓ. ም ጀምሮ በክፍያዎቹ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ በመጨመር ደንበኞቹን እንደሚያስከፍል አስታውቋል።
