አሜሪካ ለኢራን ብሔራዊ ቡድን ቪዛ ፈቀደች

Date:

አሜሪካ ለዓለም ዋንጫ ላለፈው የኢራን ብሔራዊ ቡድን ስፖርተኞችና የቡድን አባላት ቪዛ መስጠቷን አስታወቀች። የኢራን ብሔራዊ ቡድን የመጀመሪያ ጨዋታውን በሎስ አንጀለስ ከተማ ከኒው ዚላንድ ጋር እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን፣ የአሜሪካ ባለሥልጣናት ግን ውሳኔውን ያስተላለፉት ጥብቅ ጥንቃቄ በማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።

“የኢራን ብሔራዊ ቡድን ሥርዓቱን በመበዝበር አሸባሪዎችን ወደ አሜሪካ እንዲያስገባ አንፈቅድም” ሲሉ ባለሥልጣናቱ ማስጠንቀቂያ አዘል መልዕክት አስተላልፈዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢራን እግር ኳስ ፌደሬሽን ስለ ቪዛው መሰጠት እስካሁን በይፋ የሰጠው መግለጫ የለም። ይህ ክስተት በዓለም ዋንጫ ታሪክ ውስጥ አንዲት አስተናጋጅ አገር በጦርነት ውስጥ ከምትገኝ አገር ጋር ያላትን የፖለቲካ ውጥረት ወደ ጎን በመተው ብሔራዊ ቡድኑን ስትቀበል የመጀመሪያው ያደርገዋል፤ ይህም በስፖርቱ ዓለም ከፍተኛ ትኩረት ስቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...