አሜሪካ እና ኢራን ለስምምነት ቢቃረቡም የማያግባቧቸውን ጉዳዮች መፍታት እንዳለባቸው ተገለጸ

Date:

አሜሪካ እና ኢራን ስምምነት ላይ ከመድረሳቸው በፊት በርካታ የማያግባቧቸውን ጉዳዮች መፍታት እንዳለባቸው ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ተናገሩ።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስምምነት ለመፈረም ተቃርበው እንደሆነ ከቢቢሲ የተጠየቁት ጄዲ ቫንስ፤ አሁን ላይ መናገር እንደማይቻል ገልጸዋል።

ሁለቱ አገራት ስምምነት ላይ ከደረሱ የተኩስ አቁሙ በ60 ቀናት ይራዘማል። ስለ ኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብርም ንግግር ይጀመራል።

ኢራን እና አሜሪካ የስምምነት ማዕቀፍ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን የዋሽንግንተን ባለሥልጣናት ትናንት ሐሙስ ለቢቢሲ መግለጻቸው ይታወሳል።

ሆኖም የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል ስምምነቱ እንዳልተጠናቀቀ እና እንዳልተረጋገጠ ገልጿል።

የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ “ዩራኒየም የማበልጸግ ጉዳይን ጨምሮ በአንዳንድ ነጥቦች ዙርያ” ድርድሮች እየተካሄዱ መሆኑን ተናግረዋል።

ስምምነት ላይ ተደርሶ እንደሆነ ተጠይቀውም “እዚያ ነጥብ ላይ አልደረስንም፤ ግን ተቃርበናል። አሁንም ሥራችንን እንቀጥላለን” ብለው መልሰዋል።

ኢራን ዩራኒየም ማበልጸግ እንድታቆም እና እስካሁን ያከማቸችውን እንድታስወግድም አሜሪካ ጠይቃለች።

ሁለቱ አገራት የተኩስ አቁም ካደረጉ ወዲህ ውይይታቸው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ እንደሆነ ትራምፕ ሲናገሩ ተደምጧል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...