አቶ ታዬ ደንደአ “እጃቸው በካቴና እንዲታሰር ባለመፍቀዳቸው” ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ

Date:

የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ እጃቸው ላይ ካቴና ለማስገባት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በፍርድ ቤት ቀጠሯቸው ላይ ሳይገኙ ቀሩ።


አቶ ታዬ ደንደአ ረቡዕ ታኅሣሥ 22/2018 ዓ.ም. ልደታ በሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡባቸውን ሦስት ክሶች ለማየት ቀጠሮ ተይዞላቸው ነበር።


ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ይዞ የነበረው የዐቃቤ ሕግን ክስ እና የተከሳሹን ተቃውሞ ለመስማት ነበር።
ይሁን እንጂ የአቶ ታዬ ደንደአ ጠበቆች በችሎቱ ላይ ቢገኙም እርሳቸው ግን ሳይገኙ ቀርተዋል።


የማረሚያ ቤቱ የፖሊስ መኮንኖች ለችሎቱ አቶ ታዬ ደንደአ እጃቸው ላይ ‘ሰንሰለት ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው’ ፍርድ ቤት እንደማያቀርቡ ተናግረዋል።


አቶ ታዬ ቀደም ሲል በአለርጂ ምክንያት ሰንሰለት ማድረግ እንደማይፈልጉ ተናግረው ነበር።
ፍርድ ቤቱ በበኩሉ የማረሚያ ቤት ፖሊስ ተከሳሹን በ’ጥቃቅን ምክንያቶች’ ወደ ፍርድ ቤት አለማቅረቡ ስህተት መሆኑን ተናግሯል።
ችሎቱ አቶ ታዬ ደንደአ ሐሙስ ታኅሣሥ 23/2018 ዓ.ም. ችሎት ፊት እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።


አቶ ታዬ ከቀረቡባቸው ሦስት ክሶች በሁለቱ ነጻ ሲባሉ የጦር መሣሪያ ሕግን በመተላለፍ በቀረበባቸው ክስ ግን ጥፋተኛ ተብለው የሰባት ዓመት ከሁለት ወር እስር ተፈርዶባቸዋል።


አቶ ታዬ ነጻ የተባሉባቸው ክሶች “ከጠላት ጋር ማበር” አና የአገር መከላከያ ሠራዊትን ለመምታት “ዝግጅት አድርገዋል” የሚሉት ሁለት ከባድ ክሶች ናቸው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...