አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ከሰጠው 50 ሚሊየን ብር ስጦታ ተጨማሪ የሚሆን ክለባችን ያለበትን የውጪ ተጨዋቾች ደመወዝ ክፍያ፣ወለድ እና ቅጣት መክፈያ የሚሆን ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓም ገቢ አድርገዋል፡፡
ይህንን ተከትሎም ክለባችን ያለበትን እዳ ከመክፈሉም በላይ በፊፋ የተጣለበትን የተጫዋቾች ምዝገባ እገዳ የሚነሳለት ይሆናል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ የምዝገባ እገዳው ከተነሳለት በኋላ እየተካሄደ ላለው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና ለሚመጣው የውድድር ዘመን ተጫዋቾችን መመዝገብና ማስፈረም ይችላል፡፡
አቶ ጀማል አህመድና ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ክለባችን ቅዱስ ጊዮርጊስ በሚፈልገው ሁሉ የማይተካ ድጋፍ እያደረጉ የቀጠሉ ሲሆን ለክለቡ እድገትና ስኬት እያበረከቱ ላለው የላቀ አስተዋፅኦ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር በክለቡ እና በደጋፊዎቹ ስም የከበረ ምስጋናውን ያቀርባል።
#ይሄነውጊዮርጊሳዊነት
አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ
Date:
