ኢራን እና አሜሪካ አንዳቸው የሌላኛቸውን የጦር መርከብ መምታታቸውን ተናገሩ

Date:

አሜሪካ የኢራን የጦር መርከብን ማስጠሟን ስትገልጽ፤ ኢራን ደግሞ በግዙፉ የአሜሪካ አውሮፕላን ተሸካሚ መርከብ ላይ በባለስቲክ ሚሳዔሎች ጥቃት መፈጸሟን አስታውቃለች።

የአሜሪካ ሠራዊት ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) በኤክስ ገጹ ላይ እንዳስታወቀው በኢራን ላይ ጥቃት በተጀመረበት ቅዳሜ ዕለት የኢራን የጦር መርከብን መትቶ ማስጠሙን ገልጿል።

“መርከቡ በኦማን ሰላጤ አካባቢ ባለ የባሕሩ ክፍል ላይ እየሰጠመ ነው” ሲል ሴንትኮም ጨምሮ ገልጿል።

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ደግሞ በባሕረ ሰላጤው ተሰማርቶ በሚገኘው የአሜሪካ የጦር አውሮፕላን ተሸካሚ መርከብ አብርሃም ሊንከን ላይ በአራት ተወንጫፊ ሚሳዔሎች ጥቃት መፈጸሙን የኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ይህንን ተከትሎ የአሜሪካ ሠራዊት ማዕከላዊ ዕዝ የጦር መርከቡ በኢራን ሚሳዔል ተምትቷል መባሉን “የተተኮሱት ሚሳዔሎች አጠገቡም አልደረሱም” በማለት አስተባብሏል።

ጨምሮም አብርሃም ሊንከን የጦር መርከብ “ከኢራን አገዛዝ ከሚፈጠር ስጋት የአሜሪካ ሕዝብን ለመከላከል በሚካሄደው ያልተቋረጠ ዘመቻ” ላይ የሚሰማሩ አውሮፕላኖችን በማስተናገድ ላይ መሆኑን ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...