ከ2.4 ሚሊዮን በላይ የወባ በሽታዎች እና 103 ሰዎች ሞት ሪፖርት ተደረገ

Date:

በ2025 የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ባለው ጊዜ ውስጥ ከ2.4 ሚሊዮን በላይ የወባ በሽታዎች እና 103 ሰዎች ሞት መመዝገቡ ተገለጸ። ይህ የወባ ወረርሽኝ በዋነኛነት በኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ምዕራብ ክልሎች ላይ መከሰቱን ካፒታል ከዩኒሴፍ አዲሱ ሪፖርት ተመልክቷል።

በዚሁ ጊዜ ውስጥ በአማራ እና ጋምቤላ ክልሎች ከ4,373 በላይ የኮሌራ በሽታዎችና 42 ሰዎች ሞት መመዝገቡም ታውቋል።

በሀገሪቱ የውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር 3.3 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ አብዛኞቹ በግጭት (69%) እና በድርቅ (17%) ምክንያት የተፈናቀሉ መሆናቸውን ሪፖርቱ አሳይቷል።

ዩኒሴፍ እንዳስታወቀው በ2025 የመጀመሪያ አጋማሽ ለአምስት ዓመት በታች ለሆኑ 331,000 ህጻናት የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሕክምና ሰጥቷል። ከ2.3 ሚሊዮን በላይ ሴቶች እና ህጻናት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አገልግሎት ሲያገኙ፣ ከ1.4 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ደግሞ ንጹህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ መሆናቸውን አመልክቷል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...