የማሌዢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢትዮጵያ ገቡ

Date:

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሶስት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡት። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ፤ ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከተቀበሉ በኃላ ” ወደ ምድር ቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን ደህና መጡ ” ብለዋል።

” ጉብኝትዎ በማሌዢያ እና ኢትዮጵያ መካከል እያደገ ያለውን ወዳጅነት እና ትብብር የሚያሳይ ሲሆን በሀገራችን የብልጽግና ጉዞ ውስጥም በጠቃሚ ጊዜ የተደረገ ጉብኝት ነው ” ሲሉ አክለዋል።

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ከአመት በፊት በማሌዢያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አድርገው እንደነበር ይታወሳል። በወቅቱም ከጠቅላይ ሚኒስትር አንዋር ኢብራሂም ጋር ውይይት አድርገው ነበር።

በወቅቱም በግብርና፣ ማዕድን፣ ማኑፋክቸሪንግ እና ታዳሽ ኃይል ላይ ትኩረታቸውን ያደረጉ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሁም ሌሎች ቁልፍ ሥራዎች ላይ የሚሰሩ ስራዎችን ለማጠናከር ስምምነት አድርገው ነበር።

በተጨማሪም የማሌዢያ የንግድ ማኅበረሰብ በፍጥነት በመስፋፋት ላይ ባለው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን የኢንቬስትመንት እድል እንዲጠቀሙ ፤ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበው ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...