የኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የልህቀት ማማ የሆነው ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ከዓለማችን ግዙፍ የአውሮፕላን አምራች ቦይንግ ኩባንያ ጋር በጋራ ለመሥራት የጀመረው አዲስ ጉዞ በአፍሪካ የኤሮስፔስ ኢንዱስትሪ ላይ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
ይህ ታሪካዊ ስምምነት በዩኒቨርሲቲው አዲስ ለተቋቋመው የኢቪዬሽን ሳይንስ እና ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ አካዳሚ የቴክኖሎጂና የሰው ኃይል አቅምን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የመማሪያ ክፍሎችን ዘመናዊ ከማድረግ ባለፈ፣ በመምህራን ሥልጠና እና በተማሪዎች የፈጠራ ተሰጥኦ ላይ ትኩረት ያደረገ “የኤሮስፔስ ኢንኖቬሽን ቻሌንጅ” ይካሄዳል።
ቦይንግ እንደሚተነብየው አፍሪካ በሚቀጥሉት ሁለት አስርት ዓመታት ከ74,000 በላይ አዳዲስ የኢቪዬሽን ባለሙያዎች ያስፈልጓታል።
በመሆኑም ይህ አጋርነት የጅማ ዩኒቨርሲቲን የአፍሪካ የኤሮስፔስ የልህቀት ማዕከል በማድረግ፣ አህጉሪቱ የሚጠበቅባትን የባለሙያ ፍላጎት በራስ አቅም እንድትሞላ መንገድ ጠራጊ ይሆናል።
ይህም ኢትዮጵያ በአየር መንገድ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን፣ በኤሮስፔስ ትምህርትና ምርምርም የአፍሪካ መሪ ሆና እንድትቀጥል የሚያስችል አርቆ አሳቢ እርምጃ ነው።
