የፓኪስታን ንግዶች ወደ ቡናና ጨርቃጨርቅ እንዲገቡ ተጠየቀ

Date:

በኢትዮጵያና በፓኪስታን መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ 133 ሚሊዮን ዶላር መድረሱን ተከትሎ፣ የፓኪስታን ንግዶች እንደ ቡና፣ የቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬዎች፣ ጨርቃጨርቅና የቆዳ ውጤቶች ያሉ የኢትዮጵያ ምርቶችን በስፋት እንዲጠቀሙባቸው ጥሪ ቀረበ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ደኤታ አቶ አብዱልሃኪም ሙሉ እንደተናገሩት፣ እ.ኤ.አ በ2024 ዓ.ም. ከተመዘገበው አጠቃላይ የ133 ሚሊዮን ዶላር የንግድ ልውውጥ ውስጥ፣ የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ድርሻ 74.4 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ወደ ሀገር ዉስጥ ያስገባችው ድርሻ ደግሞ 58.6 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል።

ሚኒስትር ደኤታው ይህንን የገለጹት ከፓኪስታን ንግድ ልማት ባለሥልጣንና በፓኪስታን የኢትዮጵያ ኤምባሲ የንግድ ክፍል ጋር በመተባበር 5ኛውን የፓኪስታንና የአፍሪካ የንግድ ልማት ጉባዔና የፓኪስታን ምርቶች ኤግዚቢሽን፣ ጥቅምት 6 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚሊኒየም አዳራሽ ባስጀመረበት ወቅት ነው።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...

በፌደራሉ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መቀስቀሱ ተገለጸ

ከሱዳን ጋር በሚዋሰነው የሰሜናዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ በሚገኝ...

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...