ፑቲን ሩሲያ ብሔራዊ ጥቅምን ከማክበር ጋር በተያያዘ ከአሜሪካ ምላሽ እንደምትጠብቅ ገለጹ

Date:

ፕሬዝዳንቱን ጨምሮ አሜሪካውያን እና የአሜሪካ መሪዎች የራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም አላቸው እኛም የነርሱን ፍላጎት እናከብራለን ብለዋል፡፡

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸው አንዳቸው የሌላውን ብሄራዊ ጥቅም መከባበርን በተመለከተ ከአሜሪካ ምላሽ እንደምትጠብቅ ተናግረዋል።

ፑቲን ከሩሲያዉ ጋዜጠኛ ፓቬል ዛሩቢን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ አሜሪካውያን የአሜሪካ ህዝቦች እና የአሜሪካ መሪዎች የራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም አላቸው፣ እኛም እናከብራለን ብለዋል።

ይህ አስተያየት የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፑቲን እና ከዩክሬን አቻቸው ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በዩክሬን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ ለመነጋገር ባቀዱበት ወቅት ነው።

ትራምፕ በኢስታንቡል በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ከፍተኛ ደረጃ ያለው የሰላም ድርድር አመቻችተዋል፡፡

ሁለቱም ወገኖች እያንዳንዳቸው 1 ሺህ የጦር እስረኞችን ለመለዋወጥ እና የእርቅ ስምምነት ለማድረግ ድርድሩን ለመቀጠል ተስማምተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...

የብሔር ፌደራሊዝምን ለማስቀጠል “የቆረጡ” ተመካካሪዎች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 14ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች የአጀንዳ...

“የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው” ፓትርያርኩ

የሩሲያ ክርስቲያኖች ከኢራን ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው...