ሀማስ ያልተቀበለው ውሳኔ

Date:


የአውሮፓ ህብረት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት የጋዛን ግጭት ለማስቆም ያሳለፈውን ውሳኔ እንደተቀበለው አስታወቀ ።

የጋዛን ግጭት እስከወዲያኛው ይፈታል ተብሎ የታመነበትን ባለ20 ነጥብ የሰላም ዕቅድ ለቀጣናው አጠቃላይ ገፅታ አስፈላጊ መሆኑን ህብረቱ ገልጿል ።

የአውሮፓ ህብረት ቃል አቀባይ አኑዋር ኤል አኖኒ በብራሰልስ በሰጡት መግለጫ ፣ የተመድ ውሳኔ ሰብዓዊ እርዳታ በሚገባበት ፣የመልሶ ግንባታ በሚካሄድበት እና ተቋማዊ እድሳት በሚከናወንበት ሁኔታ መምከሩ እና ውሳኔ ላይ መድረሱ ትልቅ እርምጃ ነው ሲሉ አወድሰውታል ።

ህብረቱ ከተመድ እና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመሆን በጋዛ አስተማማኝ ሰላም እንዲኖር ይሰራል ብለዋል ቃል አቀባዩ ።

ምን እንኳ የፀጥታው ምክር ቤት በጋዛ የሰላም እና ደህንነት አስከባሪ ሀይሎች እንደሚገቡ ከውሳኔ ቢደርስም ሀማስ ግን ውሳኔውን አልተቀበለውም ተብሏል ።

ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...