ስብሰባው ያተኮረው ኢትዮጵያ በደቡባዊ የአገሪቱ ክፍል በተከሰተው የማርበርግ የቫይረስ በሽታ አጠቃላይ እና ፈጣን ምላሽ መስጠት ላይ ነው።
ዶ/ር መቅደስ የበሽታውን የላብራቶሪ ምርመራ ፣ ከታማሚዎች ጋር የነበሩ ንክኪዎች ክትትል፣ የአደጋ ዝግጁነት እና የማህበረሰብ ተሳትፎን ጨምሮ አስቀድመው የተተገበሩ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎችን አብራርተዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት በኢትዮጵያ አምባሳደር ማሲንጋ በበኩላቸው የኢትዮጵያን ጠንካራ እና ወቅታዊ እርምጃ አድንቀዋል።
የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመከላከል እና በመቆጣጠር ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግም የአሜሪካ መንግስት ዝግጁ መሆኑን አምባሳደር ማሲንጋ ገልጸዋል።
