ሁለት ባንኮች በኢትዮጵያ የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኙ

Date:



ሲቢኢ ካፒታል አክሲዮን ኢንቨስትመንት ባንክ እና ወጋገን ካፒታል አክሲዮን ማህበር ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ ያገኙት የመጀመርያው የኢንቨስትመንት ባንኮች ናቸው።

እነዚህ ባንኮች እራሳቸውን ችለው የተቋቋሙ የካፒታል ገበያ ስራ ብቻ የሚሰሩ የኢንቨስትመንት ባንኮች ናቸው።

በተጨማሪም ለአምስት የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጭዎች ፈቃድ ተሰጥቷል።

ፈቃድ የተሰጣቸው አገልግሎት ሰጪዎች ህጉ የሚጠይቃቸውን መስፈርቶችና መመዘኛዎች አሟልተዋል ተብሏል።

ይህንን ፈቃድ አስመልክቶ ዛሬ የኢትዮዽያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እና የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ቦርድ ሰብሳቢ ማሞ ምህረቱ አብስረዋል።

የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገበያው  የሀገሪቱን የክፍያ ሚዛን ያረጋጋል ከውጭ ብድር ጥገኝነትና የውጭ ብድር በመቀነስ የማክሮ ኢኮኖሚ ማረጋጋትን ይፈጥራል ብለዋል።

ታማኝነት ያለው የፋይናነስ ሥርዓት ለመገንባት የተዘረጋው የካፒታል ገበያ፤ ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት ለመፍጠር ያግዛል ተብሏል።

ገበያው አዲስ እንደመሆኑ መጠን ለመቆጣጠር ብቻ ሳይሆን ከሚመለከታቸው ጋር አብሮ ለመስራት እድል መፈጠሩ ተነግሯል።

የኢንቨስትመንት ባንኮችና የሰነደ ሙአለ ነዋይ ኢንቨስትመንት አማካሪዎችን  ጨምሮ ዛሬ ፈቃድ ያገኙ የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች በድምሩ ዘጠኝ ደርሰዋል።

የኢትዮዽያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀና ተኸልቁ ዛሬ ፈቃድ የተሰጣችሁ በሙሉ ስራችሁ ሀላፊነት የተጣለበት በመሆኑ ህጉን አክብራችሁ እንድትሰሩ ሲሉ አሳስበዋል።

እነዚህ የኢንቨስትመንት ባንኮች ከንግድ ባንኮች የሚለዩ ሲሆን ቁጠባን አያሰባስቡም፤ ብድር አይሰጡም።

በምትኩ ኢንቨስትመንትን በማማከር በሌሎች የካፒታል ገበያ ስራዎች መሳተፍ እንደሚችሉ ሰምተናል።

ከሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግብጻዊቷ የቴሌቪዥን አዘጋጅ በዕፅ ዝውውር ወንጀል የሞት ፍርድ ተወሰነባት

የካይሮ የወንጀል ችሎት፤ ዕውቋን የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅ ሳራ ካሊፋን...

ከአሜሪካ ጋር የሚኖረው “የጨዋታው ሕግ ተቀይሯል፤ የተመጣጠነ ምላሽ ዘመን አብቅቷል

ኢራን ከአሜሪካ በኩል ለሚሰነዘርባት ጥቃት የምትሰጠው ተመጣጣኝ የአጸፋ ምላሽ...

የ2.5 ቢሊየን ብር ግዙፍ ፕሮጀክት በአታ ለማርያም ገዳም በመስከረም ወር የመሠረት ድንጋይ ሊያኖር ነዉ

​በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ የታዕካ ነገሥት...

የዲቪ ዕድለኞች የማመልከቻ ሂደታቸውን እንዲቀጥሉ ተወሰነ!

የአሜሪካ የፌዴራል ፍርድ ቤት በዲቪ ሎተሪ አመልካቾች የማመልከቻ ሂደት...