ሁለት ቤተመንግስቶች የባለ አምስት ኮከብ ሆቴል አገልግሎት መስጠት ሊጀምሩ ነው

Date:

በኢትዮጵያ ቤተመንግስት አስተዳደር ስር የሚተዳደሩት ድሬዳዋ ቤተ መንግስት እና የጅማ ግቤ አዳራሽ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል የሚያደርጋቸው ግንባታ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ መድረሱን አራዳ ከኢትዮጵያ ቤተ መንግስት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ምትኩ ኩምሳ ሰምቷል።

የድሬዳዋ ቤተመንግስት የሆቴል ግንባታው ከሦስት ዓመታት በፊት ተጀምሮ አሁን ወደ መጠናቀቂያው ምዕራፍ ላይ ደርሷል ተብሏል።

በጅማ የሚገኘው ግቤ አራዳሽ የሆቴሉ ግንባታ በሸራተን አዲስ ሆቴል ድርጅት የተከናወነ ሲሆን፣፥ ሸራተን ኢንቨስት ያደረገበትን ሆቴል ለሦስት ዓመታት ወጪውን ለመተካት ከተገለገለበት በኋላ ለቦታው የኪራይ ክፍያ ለመንግስት መፈፀም እንደሚጀምር ተመላክቷል።

በሁለቱም ቤተመንግስቶች ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ የኢትዮጵያ ንጉስ ሳሉ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ቤቶች የቅርስ ይዘታቸው ሳይነካ ተጨማሪ ግንባታዎችን በማከል ለአገልግሎት ዝግጁ እየተደረጉ መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...