ሃማስ ከእስራኤል ጋር ያቋረጠውን ድርድር ለመቀጠል ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ

Date:

ሃማስ ከእስራኤል ጋር አቋርጦት የነበረውን የዶሃ ድርድር ለመቀጠል ፈቃደኛ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ሃማስ ፈቀደኝነቱን የገለጸው እስራኤል በአዲስ መልኩ በቡድኑ ላይ መጠነ ሰፊና የተጠናከረ ጥቃት መክፈቷን ተከትሎ ነው ተብሏል፡፡
እስራኤል የቀሩ ታጋቾችን ለማስለቀቅ በሚል በጀመረቸው ወታደራዊ ዘመቻ በ150 የቡድኑ ወታደራዊ ይዞታዎች ላይ ጥቃት መፈጸሟ ተሰምቷል፡፡

ከእስራኤል የቀናት ጥቃት በኋላም በኳታር ዶሃ የሚገኘው የሃማስ ተዳራዳሪ ልዑክ ከእስራኤል ጋር ቀደም ሲል ያቋረጠውን ንግግር ለመቀጠል ፈቃደኛ መሆኑን ገልጿል፡፡
የእስራኤል ተደራዳሪ ልዑክም የሃማስ ልዑክ ያሳየውን ፈቃደኝነት ተከትሎ ዛሬ ምሽት ወደ ኳታር እንደሚያቀና ተመላክቷል፡፡

ቀጥተኛ እንዳልሆነ የተነገረለት የዶሃው ድርድር ከወትሮው በተለየ ተስፋ ባይጣልበትም ፤ ሁለቱን ወገኖች ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ሊወስድ እንደሚችል መጠቆሙን ሚድል ኢስት ሞኒተር ዘግቧል፡፡

በመጀመሪያ ዙር በተደረገው ድርድር ሃማስ ቀሪ 58 ታጋቾችን ለመልቀቅ በእስራኤል የቀረበውን ሃሳብ ባለመቀበሉ አስራኤል በቡድኑ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት አጠናክራ መቀጠሏ የሚታወስ ነው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...