“ሄር ስቶሪ” የሥነ-ጥበብ ዐውደ ርዕይ ተከፈተ

Date:

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በልዩ ሁኔታ ለማክበር ያለመውና “ሄር ስቶሪ” የተሰኘው የጋራ የሥነ-ጥበብ ዐውደ ርዕይ፣ ባሳለፍነው ቅዳሜ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በ“ዘ ስፔስ ኢትዮጵያ” ጋለሪ በድምቀት ተከፍቷል።

በታዋቂ እና ተስፋ ሰጪ ሴት ሰዓሊያን ማለትም በአሌክሳንድራ ምትኩ፣ ብሌን ደረሰ፣ ፍቅርተ አያና፣ ምሕረት እሸቱ፣ ኒና ኡርጌሳ፣ ራፋኤላ ፍቃዱ፣ ሩት አስክንድር እና ሩት ጌታቸው የፈጠራ ሥራዎች የተሞላው ይህ ዐውደ ርዕይ፤ ለቀድሞዋ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ መታሰቢያነት የተበረከተ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

የሴቶችን ሁነኛ ታሪክና የጥበብ አሻራ በሥዕል የሚተርከው ይህ ዝግጅት፣ እስከ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተመልካቾች ክፍት ሆኖ የሚቆይ በመሆኑ፣ የጥበብ አፍቃሪያን ዕድሉን ተጠቅመው እንዲጎበኙ ተጋብዘዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...