የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥ ለታዋቂው አሜሪካዊ የአንትሮፖሎጂ እና የሰው ልጅ አመጣጥ ጥናት ምሁር የክብር የሳይንስ ዶክትሬት ዲግሪ እንዲበረከት ውሳኔ አስተላልፏል።
🇪🇹 ዩኒቨርሲቲው ይህንን ከፍተኛ ዕውቅና የሰጠው ምሁሩ በሰው ልጅ ዝግመተ ለውጥ ሳይንስ ዘርፍ ላበረከቱት የዕድሜ ልክ አስተዋፅዖ እና ኢትዮጵያ የሰው ልጅ መገኛ ምድር መሆኗን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ ላደረጉት ታላቅ ሚና ነው ብሏል።
☠️🤩ፕሮፌሰር ጆሃንሰን እ.ኤ.አ. በ1974 በኢትዮጵያ አፋር ክልል (ሃዳር) ውስጥ “ሉሲ” ወይም “ድንቅነሽ” በመባል የምትታወቀውን የ3.2 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ ያላትን የሰው ዘር ቅሪተ አካል በማግኘት የሰው ልጅ አመጣጥ ታሪክን የቀየረ ሳይንሳዊ ግኝት ማሳካታቸው ይታወሳል።
👉 በአሁኑ ወቅት በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ የክብር ፕሮፌሰር እና የሰው ልጅ አመጣጥ ጥናት ተቋም መሥራች ዳይሬክተር የሆኑት ጆሃንሰን፥ የኢትዮጵያን የቅሪተ አካል ቅርሶች ለመጠበቅና ለማስተዋወቅ ላደረጉት የላቀ ውሳኔ ተቋሙ ምስጋና አቅርቧል።
