ላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ለሶስት ቀናት የሚቆይ  የዳሌና ጉልበት መገጣጠሚያ  ንቅለ ተለካ እየሰጠ ይገኛል

Date:

ላለፉት አስራ ሰባት አመታት የተለያዩ ሕከምና አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ላንድማርክ  አጠቃላይ ሆስፒታል በሕንድ ሀገር ከሚገኘው ፎርቲስ ከተባለ ሆስፒታል ጋር በመተባባር ከሐምሌ 21 እስከ 23 ቀን 2017ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ህክምና እየሰጠ መሆኑን አስታዉቋል።

የዳሌና ጉልበት መገጣጠሚያ ቅየራ ንቅለ ተለካ ህክምናው የሚሰጠው  ከህንድ  ሀገር ልምድ ያካበቱ ባለሙያዎች በማስመጣት እንደሚሰጥ ተገልፆል፡፡

ሆስፒታሉ ከፎርቲስ ሆስፒታል ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር  የፎርቲስ ሆስፒታል ተወካይ ቢሮ መከፈቱ ተነግሯል፡፡ የንቅለ ተከላው አገልግሎት የሚሰጠው ለሦስተኛ ዙር መሆኑን የተነገረ ሲሆን የሚመጡ ታካሚዎች እንደየ ወረፋቸው የሚስተናገዱ እና ዋጋው ተመጣጣኝ ነው ሲሉ የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ፕሮፌሰር ከበደ ወሌአያና  ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

ቀዶ ህክምናው በሦስት ዶክተሮች እንደሚሰጥ የተገለፀ ሲሆን በቀጣይ የሀኪሞችን ቁጥር በመጨመር የህክምና አገልግሎቱ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡

የዳሌና የጉልበት መገጣጣሚያ ሕመም መንስኤው በርካታ ሲሆን በተለይም ከእድሜ መግፋት ጋር ተያይዞ የመገጣጠሚያ መሸርሸርና መሰባበር እንዲሁም ታካሚዎች ለሌላ ሕመም በሚወስዷቸው መድሃኒቶች ምክንያት እንዲሁም በአካል ክፍሎቹ ላይ ጉዳት በሚደርስበት ጊዜ እንደሚያጋጥም ተገልጿል፡፡

በሆስቲታሉ በየዓመቱ ከ 30 እስከ 40ሺ ለሚሆኑ ታካሚዎች የተለያየ የህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልፆል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...