የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በሚያካሂደው አስቸኳይ ስብሰባው የተሻሻለውን የፌዴራል የገቢ ግብር ረቂቅ አዋጅን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል ።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ በዕለቱ የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችንም ያጸድቃል።
የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን ማጽደቅም የእለቱ አጀንዳ ነው።
እንዲሁም የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ
ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያጸድቅም ያገኘነው መረጃ ጠቁሟል።
