ሩስያ በዩክሬይን ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የራሷን ግድብ ማውደሟ ተሰማ። ሩስያ ግድቡን ያወደመችው የዩክሬይን ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎችን ለማገድ ነው ተብሏል። እጄን በእጄ ይሏል ይኼ ነው፡፡
የጀርመን ዜና አገልግሎት እንደዘገበው፤ ሩስያ ግድቡን የደረመሰችው ሦስት ቶን ይመዝናል በተባለ የጦር አውሮፕላን ቦምብ ሲሆን፤ ግድቡ ከዩክሬይን ድንበር በጥቂት መቶ ኪሎ ሜትሮች በምትገኘው ፖፖቭካ በተባለች መንደር አቅራቢያ ነው።
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፤ ዩክሬይን በቤልጎሮድ ዞን የማጥቃት እርምጃዋን እያጠናከረች ሲሆን፤ የዩክሬይን ጦር ግን በጉዳዩ ላይ እስከ አሁን ያለው ነገር የለም ተብሏል፡፡
