ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

Date:

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ እና ለዲጂታላይዜሽን ፕሮግራም የሚውል የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት መስማማቷን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡

ይህ ስምምነትየኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የአውቶሜሽን ሥርዓት ለማዘመን እና አዲስ የብሔራዊ ግሪድ መቆጣጠሪያ ማዕከልን ለመገንባት ይውላል ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ የ150 ሜጋ ዋት የጂኦተርማል (የከርሰ ምድር እንፋሎት) ኃይል ለማመንጨት አዲስ የማዕቀፍ ስምምነት ተደርጓል።

የኤሌክትሪክ መቆራረጥን በ 50 በመቶ በመቀነስ ከ4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተሻለ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር የሚያስችል ስለመሆኑ ተነግሩለታል፡፡

ይህ ደግሞ የካርቦን ልቀትን በ150 ሺህ ቶን በመቀነስ የአካባቢ ጥበቃ ጥረትን ያግዛል።

ስምምነቱ  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ በአውሮፓ ህብረት እና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲዎች (AFD) በትብብር የሚተገበር ሲሆን የሀገሪቱን  የኢነርጂ ዘርፍ ወደ ተሻለ ዲጂታል ከፍታ እንደሚያሸጋግረው ታምኖበታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...

“ሺ ጂምፒንግ ምርጥ መሪ ነው!”- ትራምፕ

አሜሪካና ቻይና ተፎካካሪ ሳይሆኑ አጋርነት ያላቸው ሀገራት ናቸው አሉ...