ስለ ፕላስቲክ ምርቶች

Date:

ኢትዮጵያ በቅርቡ ተግባራዊ ያደረገችውን የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ተከትሎ፣ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የተከለከሉ የአንድ ጊዜ ብቻ አገልግለው ከሚጣሉ የፕላስቲክ ምርቶች መካከል በልዩ ሁኔታ መፈቀድ ያለባቸውን ለመለየት መረጃዎች እየተሰበሰቡ እንደሆነ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ለአሐዱ አስታውቋል።

ባለስልጣኑ አዋጁን ለማስፈጸም የሚያግዝ መመሪያ በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ የገለጹት የከተማ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ክትትል ዴስክ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ዓለሙ፣ “ተቋማት በልዩ ሁኔታ እንዲፈቀዱላቸው የሚፈልጓቸውን የፕላስቲክ ምርቶች ለይተው እንዲያቀርቡ የጊዜ ገደብ ተሰጥቷቸዋል” ብለዋል።

በዚህ ሂደት በሱፐርማርኬቶችና በመገበያያ ስፍራዎች ሕብረተሰቡ እየተጠቀመባቸው የሚገኙ ምርቶች በአዋጁ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 6 ላይ በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት፣ ይህ ልዩ ሁኔታ የፕላስቲክ ከረጢቶችን እንደማይመለከት ተገልጿል።

የፕላስቲክ ከረጢቶችን በልዩ ሁኔታ ማስገባትም ሆነ መጠቀም በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፣ ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ምርቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ በአስተዳደራዊ ውሳኔ የሚቋጭ ቢሆንም የፕላስቲክ ከረጢቶችን ማምረት፣ መጠቀም፣ መሸጥ፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት እና ማከማቸት የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ኃላፊው አጽንኦት ሰጥተውበታል።

(አሐዱ ሬዲዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...

በ’ፊንቴክ’ የማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጠ

በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ስም በተፈጸመ  የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር...

የጣሊያን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያደረጉት የኢንቨስመንት መጠን 723 ሚሊዮን ዩሮ መድረሱ ተሰማ

ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች  በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን...

የቴሌግራም ማስጠንቀቂያ

ቴሌግራም (Telegram) ኦፊሴላዊ ያልሆኑ የቴሌግራም መተግበሪያዎችን (Unofficial Apps) በሚጠቀሙ...