የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር “ስምምነት ላይ እንደርሳለን አልያም የጀመርነውን ሥራ እንጨርሳለን” ሲሉ አስጠነቀቁ።
ትራምፕ በሰጡት ቃለ ምልልስ የሆርሙዝ ወሽመጥ ቢዘጋም የነዳጅ ዋጋ ብዙም እንዳልጨመረ ተናግረዋል።
“ነዳጅ በብዛት ወስደንባቸዋል። ማንም አላወቀም፤ ይሄ የሆነው በአንድ ወር ተኩል ነው” ብለዋል።
የኢራንን ባሕር ኃይል እና አየር ኃይል ማውደማቸውን በድጋሚ ገልጸዋል።
“መቆጣጠሪያ ሥርዓት እንደሌላቸው አውቀዋል። መቆጣጠሪያ ሥርዓታቸው ስለወደመ በምሽት ዒላማ አድርገናቸዋል” ሲሉም ተናግረዋል።
ትራምፕ “ጉልበተኛው ባሕር ኃይላችን ማንም አይቶት የማያውቅ እገዳ ጥሏል። ለሁለት ወር አንድም መርከብ አላለፈም። ለስምምነት ስንቃረብ እገዳውን አላልተናል። ስምምነት ላይ እንደርስ ይሆናል” ሲሉም አክለዋል።
“ዞሮ ዞሮ እናሸንፋለን። ወይ እንስማማለን ወይም ሥራውን እንጨርሳለን” ብለዋል ፕሬዝዳንቱ።
91 ሚሊዮን የኢራን ሕዝብ “እንዲጎዳ ስለማይፈልጉ” ስምምነት ላይ መድረስን እንደሚመርጡ ገልጸዋል።
