ስምንት ሺህ የልብ ህሙማን ታካሚዎች ህክምና ለማድረግ ወረፋ እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ማህበር በ2024 በጀት ዓመት ከ12 ሺህ በላይ የተመላላሽ የልብ ሕክምና ክትትል እና 669 ለሚጠጉ ታካሚዎች ደግሞ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን አስታውቋል።

ለታካሚዎች የሰጠው አገልግሎት በገንዘብ ሲተመን ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ የልብ ቀዶ ሕክምና እና በ ደም ስር በኩል የሚሰጥ  የህክምና አገልግሎት መሆኑን  በኢትዮጵያ  የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ  ማዕከል የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን  ክፍል ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ዳዊት እሸቱ ተናግረዋል ።

ማዕከሉ ምንም እንኳን ነጻ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ቢሆንም አንድ ቀዶ ህክምና ለመስራት ተቋሙ የሚያወጣው  ወጪ ከ100 ሺህ ብር በላይ እንደሚሆን ተጠቁሟል። አንድ ታካሚ መጀመሪያ ከታየበት ቀን አንስቶ ቀዶ ህክምና እስከሚሰራበት  ቀን ድረስ ለዓመታት ወረፋ ሊጠብቅ  እንደሚችል ተጠቁሟል።

በተጨማሪም በተያዘው በ2025 ዓመት   ከ17,000 በላይ ለሚሆኑ ታካሚዎች አገልግሎት  ለመስጠት እንዲሁም 352 የልብ ቀዶ ህክምና እና 334  በደም ስር በኩል የሚሰጥ ህክምና ለመስጠት በዕቅድ መያዙን ተጠቁሟል። በአሁን ሰዓት አጠቃላይ ታካሚዎች ቁጥር 20 ሺህ ሲሆን ወረፋ የሚጠብቁ ታካሚዎች ደግሞ ስምንት ሺህ መሆናቸውን አንስተዋል። ይሁን እና ተቋሙ ለህክምናው  የሚያስፈልጉ  እቃዎችን ለማሟላት ችግር እንደሆነባቸው ገልጸዋል። በተለይም መድሃኒቶች  በበቂ ሁኔታ አለመኖራቸው በታቀደው ልክ ህክምና  መስጠት  እንዳይቻል  ትልቅ ተግዳሮት መሆኑን ዶክተር ዳዊት እሸቱ ጨምረው ብሥራት ሬዲዮ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...