ስምንት ሺህ የልብ ህሙማን ታካሚዎች ህክምና ለማድረግ ወረፋ እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ተገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ማህበር በ2024 በጀት ዓመት ከ12 ሺህ በላይ የተመላላሽ የልብ ሕክምና ክትትል እና 669 ለሚጠጉ ታካሚዎች ደግሞ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን አስታውቋል።

ለታካሚዎች የሰጠው አገልግሎት በገንዘብ ሲተመን ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ የልብ ቀዶ ሕክምና እና በ ደም ስር በኩል የሚሰጥ  የህክምና አገልግሎት መሆኑን  በኢትዮጵያ  የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ  ማዕከል የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን  ክፍል ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ዳዊት እሸቱ ተናግረዋል ።

ማዕከሉ ምንም እንኳን ነጻ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ቢሆንም አንድ ቀዶ ህክምና ለመስራት ተቋሙ የሚያወጣው  ወጪ ከ100 ሺህ ብር በላይ እንደሚሆን ተጠቁሟል። አንድ ታካሚ መጀመሪያ ከታየበት ቀን አንስቶ ቀዶ ህክምና እስከሚሰራበት  ቀን ድረስ ለዓመታት ወረፋ ሊጠብቅ  እንደሚችል ተጠቁሟል።

በተጨማሪም በተያዘው በ2025 ዓመት   ከ17,000 በላይ ለሚሆኑ ታካሚዎች አገልግሎት  ለመስጠት እንዲሁም 352 የልብ ቀዶ ህክምና እና 334  በደም ስር በኩል የሚሰጥ ህክምና ለመስጠት በዕቅድ መያዙን ተጠቁሟል። በአሁን ሰዓት አጠቃላይ ታካሚዎች ቁጥር 20 ሺህ ሲሆን ወረፋ የሚጠብቁ ታካሚዎች ደግሞ ስምንት ሺህ መሆናቸውን አንስተዋል። ይሁን እና ተቋሙ ለህክምናው  የሚያስፈልጉ  እቃዎችን ለማሟላት ችግር እንደሆነባቸው ገልጸዋል። በተለይም መድሃኒቶች  በበቂ ሁኔታ አለመኖራቸው በታቀደው ልክ ህክምና  መስጠት  እንዳይቻል  ትልቅ ተግዳሮት መሆኑን ዶክተር ዳዊት እሸቱ ጨምረው ብሥራት ሬዲዮ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...