የሶማሊያ መንግሥት ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ጋር የተደረጉ የወደብ እና የደህንነት ትብብርን ጨምሮ ሁሉንም ስምምነቶች ማቋረጡን አስታውቋል ።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ሉዓላዊነትን፣ የግዛት አንድነትን እና የአገሪቱን የፖለቲካ ነፃነት የሚነኩ የጥላቻ ድርጊቶችን የሚመለከቱ አሳማኝ ማስረጃዎች መሰረት በማድረግ ነው ።
ውሳኔው በርበራን ጨምሮ ከወደቦች ጋር የተያያዙ ሁሉም ስምምነቶች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል ። በተጨማሪም የሁለትዮሽ የደህንነት እና የመከላከያ ትብብር ስምምነቶች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን ተገልጿል ።
የሶማሊያ መንግስት በዚህ ወቅት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም እያዳከመች ነው ሲል መክሰሱን ሮይተርስ ዘግቧል ።
