ለማህበረሰቡ በነፃ የሚሰጡ መድሀኒቶች በግል የጤና ተቋማት ውስጥ ሲሸጡ ተገኝ

Date:

በጤና ተቋማት ላይ በየአመቱ በሚደረግ ቁጥጥር ብዙ ግኝቶች መኖራቸውን የገለፁት በጤና ሚኒስቴር የጤናና ጤና ነክ ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ እንዳልካቸው ፀዳል ናቸው።

ከእነዚህም ውስጥ አንደኛውም በመንግስት በጀት ተገዝተውና ለማህበረሰቡ በነፃ የሚሰጡ መድሀኒቶችን ከመንግስት ተቀማት ወጥተው ሲሸጡ መገኘታቸውን እንደሆነም ተናግረዋል።

እነዚህ ተቋማት ላይም አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው አንስተው በተመሳሳይም በመደበኛ አሰራር ለታካሚዎች የሚውሉ መድሀኒቶች በህገወጥ መንገድ እንደሚወጡም ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በቁጥጥር ወቅት በየደረጃው በቂ የሆነ እውቀትና ችሎታ እንዲሁም የህክምና መሳሪያ ሳይኖር ነገር ግን ከአቅም በላይ የሚሰሩ ተቋማት መገኘታቸውን አንስተዋል፡፡

የንፅህና አያያዝ ስርዓቱ ላይም ከፍተኛ ችግር የታየባቸው መገኘታቸውን አንስተው ይህም በአጠቃላይ የታካሚ ደህንነት ችግር ውስጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመሆኑም አጠቃላይ በመድሀኒት አቅርቦትና ዙሪያ ያለውን ችግር ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የሚሰራው ስራ በስፋት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ስራ አስፈፃሚው አስታውቀዋል።

አሐዱ ራድዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...