የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢራን ከፍተኛ መሪን ህልፈት ተከትሎ በአዲስ አበባ በሚገኘው የኢራን ኤምባሲ በመገኘት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በኤምባሲው በተዘጋጀው የሀዘን መዝገብ ላይ በመፈረም፣ ለኢራን መንግስት እና ህዝብ ያላቸውን አጋርነት አረጋግጠዋል።
ሼክ ኢብራሂም በሰጡት መግለጫ፣ የተከሰተውን ክስተት “አሰቃቂ” ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ የመሪው ማረፍ ለኢራናውያን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም ለሚገኙ ሙስሊሞች ሁሉ ታላቅ ኪሳራ መሆኑን በመልዕክታቸው አስፍረዋል።
የኢራን ኤምባሲ በበኩሉ የጠቅላይ ምክር ቤቱ መሪ በስፍራው ተገኝተው ላሳዩት አክብሮትና የሀዘን ተካፋይነት ያለውን ምስጋና አቅርቧል።
ይህ ጉብኝት በሁለቱ ሀገራት የሃይማኖት ተቋማትና ህዝቦች መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና መንፈሳዊ ትስስር የሚያጠናክር መሆኑም ተመላክቷል።
