ሾዴ የተባለው የሸኔው መሮ ዋና ሰው ተገደለ ተባለ

Date:

ሾዴ እየተባለ የሚጠራው የሸኔው መሮ ዋና ሰው እንደሆነ የሚታወቀው መገደሉ ተገለፀ።

የመሮ ዋናው ሰው የነበረው እንዲሁም በታንዛኒያው ድርድር ከጫካ ወጥቶ ታንዛኒያ ዳሬሰላም ድረስ ከመሮ ጋር ተጉዞ የሸኔ ሽብር ቡድን ተደራዳሪ የነበረው ሾዴ በተወሰደበት እርምጃ ተገድሏል።

ሾዴ የተባለው የሽብር ቡድኑ አመራር ከታንዛኒያ መልስ የአጠቃላይ የወለጋ ዞኖች አዛዥ ተደርጎ በመሮ ተሹሞ የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ሾዴ የተገደለው ምስራቅ ወለጋ ዞን ሃሮ ሊሙ ወረዳ ገንጂ አካባቢ ከኮርማ ወንዝ ወደ ሱጊ በሚወሰደው መንገድ ላይ በሞተር ሳይክል ተደብቆ ሲጓዝ የፀጥታ ኃይሎች ባገኙት መረጃ መጋቢት 26 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ ላይ እርምጃ ተወስዶበታል።

ከሾዴ ጋር አብረው አጅበው ሲጓዙ የነበሩ በርካታ የሸኔ ሽብር ቡድን አባላትም ተደምስሰዋል።

ከሠሞኑ በሰሜን ሸዋ ዞን እና በሌሎችም አካባቢዎች የአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ክፉኛ እየተመቱ በቁጥጥር የዋሉ ሲሆን አሁንም ቢሆን የሸኔ ታጣቂዎች የመከላከያ ሠራዊቱን ምት መቋቋም ተስኗቸው እየተፍረከረኩ እጅ እየሠጡ እየተማረኩ እርምጃ እየተወሰደባቸውና እየተበተኑ ይገኛሉ።

ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...