በቅዳሜ እና እሁድ ገበያዎች ላይ ጥብቅ የዋጋ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝ ተገለጸ

Date:

በአዲስ አበባ በቅዳሜ ገበያዎች ከተቀመጠው ዋጋ በላይ እንዳይሸጥ የንግድ ቁጥጥር ኮሚቴ በየገበያው መመደቡን የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡

ነጋዴዎች ከተቀመጠላቸው ዋጋ በላይ ሲሸጡ ከተገኝ ያለ ምንም የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ሙሉ በሙሉ ከተመቻቸው ቦታም ጭምር ትስስር እንደሚቋረጥ ቢሮው ገልጿል።

በከተማው በአሁኑ ወቅት 210 ቅዳሜና እሁድ ገበያዎች እየተንቀሳቀሱ ሲሆን፤ ለበዓል 14 ተጨማሪ ባዛሮች ተዘጋጅተዋል ተብሏል።

እነዚህ ጊዜያዊ ገበያዎች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈላጊ የሆኑ ሸቀጦችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪዎች ተደራሽ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

በተለይም በበዓል ሰሞን በሕብረተሰቡ ላይ ያለውን ጫና ለማቃለል እና የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር እየተሰራ ነው ሲሉ የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ ገልጸዋል።

“ነጋዴዎችን ከአርሶ አደሩ ጋር በቀጥታ የሚያገናኙ ሲሆን ገበያዉ ከ15 በመቶ እስከ 20 በመቶ በሸቀጦች ላይ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ የከተማ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል” ሲሉ ኃላፊዋ ተናግረዋል፡፡

“ይህም ለሸማቾች የዋጋ ቅናሽ ከማድረግ ባለፈ አርሶ አደሩ  ምርቱን በተገቢዉ እንዲሸጥና ፍትሃዊ እድሎችን የሚያመቻች ነው” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የክሪፕቶ ሥራ ፈጣሪው የ15 ዓመት እስር ተፈረደበት

የቀድሞው የክሪፕቶከረንሲ ሥራ ፈጣሪ ተሰውሯል ከተባለ 40 ቢሊየን ዶላር...

5ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ...

የንግድ ሚኒስቴር 13 ምርቶችን በመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ (PVoC) እንዲያገኙ ወሰነ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ በሀገር...

ገዳ ባንክ ከ444 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች የተከፈለ ካፒታላቸውን በ2018 ዓ.ም...