በባንግላዲሽ የአየር ኃይል ጄት አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይወት አለፈ

Date:

በባንግላዲሽ ዋና ከተማ ዳካ የአየር ኃይል ማሰልጠኛ ጄት አውሮፕላን ተከስክሶ ቢያንስ 19 ሰዎች ሲሞቱ 164 ሰዎች ቆስለዋል።

አደጋው የደረሰው የF-7 BGI የተሰኘ የአየር ሀይል ጄት ለልምምድ በተነሳ በጥቂት ደቂቃ ውስጥ በዳካ በሚገኝ ትምህርት  ቤት ጊቢ  የተከሰከሰ ሲሆን ቢያንስ 19 ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል ።

ከሟቾቹ መካከልም የአውሮፕላኑ አብራሪ እና በርካታ ተማሪዎች ይገኙበታል  የተባለው ሲሆን በአደጋው ሰለባ የሆኑ ተማሪዎች

እድሜያቸው ከአራት እስከ 18 ዓመት መካከል እንደሆነ ተገልጿል ።

የአየር ኃይል ጀቱ ሚልስተን ኮሌጅ እና  ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ሲለሰከስ ተማሪዎች ትምህርት ቤት ውስጥ እንደነበሩ ተዘግቧል።

ከባንግላዲሽ አየር ኃይል ኩርሚቶላ ቤዝ ከተነሳ ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ባጋጠመው  የቴክኒክ ችግር ምክንያት አውሮፕላኑ ሊከሰከስ እንደቻለ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ሌተና ኮሎኔል ሳሚ ኡድ ዶውላ ቾውዱሪ ተናግረዋል። ዘገባው የሮይተርስ ነው

NBC Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...